የወላጆች መብት እና ግዴታ

ልጅ እንደወለዱ ወድያውኑ በነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ልጅዎን ማስመዝገብ አለብዎት። ያገቡ ከሆነ የልጁን የማሳደግ መብት በሚመለከት በሕጉ ላይ በትክክል የተቀመጠ ነው። ነገር ግን ያላገቡ ከሆኑ የልጁን የማሳደግ መብት በሚመለከት በግልዎ መብትዎን ማስከበር አለብዎት።

የወሊድ ምዝገባ

የወለዷቸውን ልጆች ሁሉንም በነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት (Zivilstandsamt) ማስመዝገብ አለብዎት። ማሳሰቢያ: ልጅዎ በተወለደበት ቦታ ባለው የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ሄደው ልጅዎን ማስመዝገብ አለብዎት። ምናልባትም ወደ መኖሪያዎ ወዳለው የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ቢሮ መሄድ ላያስፈልጎት ይሆናል።

ልጅዎ ሆስፒታል ከሆነ የተወለደው:
ሆስፒታሉ ሰነዱን ወደ የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት በቀጣይነት ይልከዋል። ይህም ማለት እርስዎ ምንም ማድረግ አይጠበቅብዎትም።

ልጅዎ ሆስፒታል ካልሆነ የተወለደው:
ልጅዎ የተወለደው ምናልባት ቤት ውስጥ ወይም ሌላ ቦታ ሊሆን ይችላል፣ ይህ ከሆነ ልጅዎን በአካል የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ያስመዝግቡት። ለማስመዝገብ 3 ቀን ይሰጥዎታል። የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤቱ ለምዝገባው ማቅረብ ያለብዎትን ሰነዶች ይነግርዎታል።

ማወቅ ያለብዎት መረጃ፣
ስዊዘርላንድ የተወለደ ልጅ ስዊዘርላንድ ስለተወለደ ብቻ ዜጋ አይሆንም። ወዲያውኑ የስዊዘርላንድ ዜግነት አይሰጠውም።

የአባትነት ዕውቅና ማረጋገጫ

አግብተው በትዳር ልጅ ወልደዋል:
ባልየው ወዲያውኑ በቀጥታ አባት መሆኑ ይመዘገባል። ምናልባት አባትየው አባት መሆኑን ከተጠራጠረ፣ ፍርድ ቤት መሄድ ይችላል እናም አባትነቱን መካድ ይችላል።

ሳይገቡ ልጅ ወልደዋል:
ባልየው ወዲያውኑ በቀጥታ አባት መሆኑ አይመዘገብም። ልጁ ከመወልዱ በፊት ወይም ከተወለደ በኋላ የነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት በመሄድ አባት መሆኑ ዕውቅና እንዲሰጠው ማድረግ ይችላል። ምናልባት አባትየው የተወለደው ልጅ፣ ልጁ መሆኑን ዕውቅና ላይሰጠው ይችላል። ይህ በሚሆንበት ግዜ የልጁ እናት ፍርድ ቤት ሄዳ አባትየው ልጁ መሆኑን እንዲቀበለው ማመልከት ትችላለች።

የወላጅ ሃላፊነት

እንደ ወላጅ መጠን ወላጆች የልጆቻቸውን ደህንነት በሚመለከት ሃላፊነታቸውን መወጣት አለባቸው። ይህም መብትና ግዴታቸው ነው (የወላጅ ሃላፊነት፣ elterliche Sorge) ። ለምሳሌ ያህል ልጆቻቸውን ማስተማርና፣ ለልጆቻቸው ህይወት የሚያስፈልገውን ተገቢውን ክፍያ መፈጸም አለባቸው። በተጨማሪም በሕጉ መሰረት ልጆቻቸው 18 ዓመት ዕድሜ እስኪሞላቸው ድረስ፣ ልጆቻቸውን መወከልን የልጆቻቸው ተጠሪ መሆን አለባቸው።

ተጋብታችሁ ከሆነ፣
ተጋብታችሁ ከሆነ ልጆቻችሁን በጋር ለማሳደግ ሁለታችሁም እኩል መብት እና ሃላፊነት አለባችሁ።

ያልተጋባችሁ ከሆነ፣
አስቀድሞ አባትየው ልጁ መሆኑን ዕውቅና መስጠት አለበት። ከዚያ በመቀጠልም ሁለቱም ተስማምተው በጋራ ልጃቸውን ለማሳደግ መወሰናቸውን (gemeinsame elterliche Sorge). በጽሑፍ መግለጽ አለባቸው። ከዚያ በፊት ግን አባትየው ልጁን በነዋሪዎች መመዝገቢያ ጽሕፈት ቤት ለልጁ ዕውቅና መስጠት አለበት። ሌላው አማራጭ፣ ከዚያ በኋላ ቆይተው ወደ ህጻናት ደህንነት ጥበቃ ጽ/ቤት (Kindesschutzbehörde, KESB) መሄድ ይችላሉ።.
በጋራ ልጃችሁን ለማሳደግ ስምምነት ላይ ካልደረሳችሁ ግን የህጻናት ደህንነት ጥበቃ ጽ/ቤት ውሳኔውን ይሰጣል።.
ይህንን በሚመለከት ጥያቄ ካለዎት ወይም እርዳታ የሚያስፈልጎት ከሆነ፣ ወደ የቤተሰብ የምክር አገልግሎት ጽ/ቤት በመሄድ የበለጠ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።


ቀለብ

ተለያይታችሁ የምትኖሩ ከሆነ፣ ይህም ቢሆንም እንኳን ሁለታችሁም በቀጣይነት ልጃችሁን መንከባከብ አለባችሁ። ማን ልጁን እንደሚያሳድግና እንደሚንከባከብ እና ማን ምን ያክል ገንዘብ እንደሚከፍል (ቀለብ፣ Unterhalt).መስማማት አለባችሁ።

ለልጃችሁ ለኑሮ የሚያስፈልገውን ቀለብ ሁለታችሁም ነው የምትከፍሉት። ምናልባት አንዱ ወላጅ ከሌላው ወላጅ የበለጠ ወይም ያነሰ መክፈል ሊኖርበት ይችላል። ወይም በጭራሽ ላይከፍሉም ይችላሉ። ምን ያህል ገንዘብ ደመወዝ እንደሚያገኙ እና ልጁን ምን ያህል እንደሚንከባከቡት፣ በሚንከባከቡት መጠን ይወሰናል። ወላጆቹ አንዳቸው ከአንዳቸው ጋር ክፍያውን በሚመለክትስምምነት ላይ መድረስ ካልቻሉ፣ ጉዳዩን ወደ ፍርድ ቤት መውሰድ ይችላሉ።

ከወላጆቹ አንዱ መክፈል ያለበትን ድርሻውን ካልከፈለ፣
ከወላጆቹ አንዱ ለልጁ ማሳደጊያ የሚሆን መክፈል ያለበትን ድርሻውን ካልከፈለ፣ የመኖሪያችሁን ኮሙዩን ድጋፍ መጠየቅ ይችላሉ። የመኖሪያችሁ ኮሙዩን ገንዘቡን እንዲሰጥዎት ይረዳዎታል። ገንዘቡ የሚገባዎት ከሆነ፣ ምናልባት ለቀለብ መሸፈኛ እንዲጠቀሙበት ሊሰጥዎት ይችላሉ። ይህም አቅርቦት በቅድሚያ በብድር መልክ ለቀለብ የሚሰጥ ሆኖ በኋላ የሚተካ/የሚቀነስ/ ነው። ይህም Alimentenbevorschussung.ተብሎ ይጠራል።