ወደ ሥራ ገበያ መግቢያ

አንድ ሰው በስዊዘርላንድ ውስጥ ስራ ተቀጥሮ እንዲሠራ ወይም ድርጅት ማቋቋም እንዲችል፣ ዜግነቱ እና ወደ ስዊዘርላንድ የመጣበት ምክንያት ይወሰናል። በማንኛውም ሁኔታ ሰራተኞች በማህበራዊ መድን ዋስትና የግድ መመዝገብ እና ታክስ መክፈል አለባቸው።.

የስራ ፈቃድ

አብዛኛውን ግዜ የመኖሪያ ፈቃድ ከተሰጠ የስራ ፈቃድ በአንድ ላይ ነው የሚሰጠው፣ ስለዚህ የስራ ፈቃድ ጥያቄ በዚሁ መልስ ያገኛል። በመሰረቱ የመኖር መብት ያላቸው ሰዎች ስዊዘርላንድ ውስጥ ስራ መስራት ይፈቀድላቸዋል። እንደ ዜግነቱ እና የስራው ርዝማኔው ታይቶ ስራ ቀጣሪው ወይም ሰራተኛው የስራ ፈቃድ ያመለክታል። እርግጠኛ ለመሆንና ለማጣራት ከዚህ በታች የተጠቀሱት ቢሮዎች ሊያግዝዎት ይችላሉ። እነዚህ ቢሮዎች በስዊዘርላንድ ውስጥ እስካሁን ላልኖሩ እና እዚህ መስራት ለሚፈልጉ ሰዎች ምክር ይሰጣሉ። እውቅና ያላቸው ስደተኞች (ፈቃድ B) እና ለጊዜው ተቀባይነት ያገኙ የስደተኛ ደረጃ ያላቸው ወይም የሌላቸው (ፈቃድ F) ያላቸው ልዩ ፈቃድ አያስፈልጋቸውም። ይሁን እንጂ የእያንዳንዱ ሥራ መጀመሪያ እና መጨረሻ ጊዜ ኦፊሴላዊ ቅጽ በመጠቀም ለካንቶኑ ሪፖርት መደረግ አለበት። (የምዝገባ ሂደት፣ Meldeverfahren) ። ሪፖርት የሚደረገው በሚሰሩበት ካንቶን ነው። ምዝግባው ነጻ ነው። ጥገኝነት ጠያቂዎች (መታወቂያ N) ያላቸው ፈቃድ ያስፈልጋቸዋል።

የግል ድርጅት

የራስህ የሆነ የግል ድርጅት ስዊዘርላንድ ውስጥ ለማቋቋም፣ ያለህ ዜግነት እንዲሁም የመኖሪያ ፈቃድ ዓይነት ወሳኝ ነው። ከEU/EFTA አገሮች ለመጡ ሰዎች እና የመኖሪያ ፈቃድ C ላላቸው ሰዎች፣ የስራ ድርጅት ለመመስረት ይቀላል። የስደተኞች አስተዳደር ጽ/ቤት (Migrationsamt) ለስደትኞች የግል ድርጅት ለመመስረት መቻል እና አለመቻሉን መረጃ ይሰጣል። በካንቶን አካባቢ ለሚቋቋሙ ድርጅቶች ሎኬሽኑንን ፕሮሞሽን ለማድረግ (Standortförderung) ተግባራዊ ድጋፍ ይሰጣል።

ጥቁር ስራ

ስራ ያለው ሰው ሆኖ የማህበራዊ የመድን ዋስትና የሌለው ፣ የስራ ፈቃድም የሌለው ወይም ገቢውን/ደሞዙን/ ታክስ የማይከፍል ሰራተኛ ከሆነ፣ በሕግ መሰረት ይቀጣል። ይህም ጥቁር ስራ (Schwarzarbeit). ተብሎ ይጠራል። ጥቁር ስራ ለቀጣሪውና ለተቀጣሪው ህጋዊ እርምጃ ያስከትላል። በተጨማሪም ሰራተኞች በአደጋ ግዜ የአደጋ ጊዜ የመድን ዋስትና እና የሽምግልና እንክብካቤ የላቸውም። ተቀጣሪው ቀጣሪው በተገቢው ሁኔታ የማያሰራው ሆኖ ከተሰማው፣ ሰራተኛው ከክፍያ ነጻ የሆነ ምክር ከሕግ ምክር አገልግሎት ጽ/ቤት (Rechtsberatungsstelle) መጠየቅ ይችላል። ቀጣሪያቸው በትክክል እየቀጠራቸው እንዳልሆነ የሚያምን ማንኛውም ሰው ነፃ የህግ ምክር አገልግሎት መስጫ ማእከል (Rechtsberatungsstelle) ማነጋገር አለበት።

ወጣቶች

በመርህ ደረጃ፣ ወጣቶች 15 ዓመት እድሜ ሲሞላቸው እንዲሰሩ ይፈቀድላቸዋል። መጠኑ ያልበዛ ቀለል ያለ ስራ /ለምሳሌ የእረፍት ግዜ ስራ/ ግን ይፈቀድላቸዋል። ወላጆች እና አሰሪዎች ወጣቶች ከአቅም በላይ ስራ እንዳይሰሩ መከታተል አለባቸው። እስከ 18 ዓመት ለሆኑ ወጣቶች ልዩ የሠራተኛ ሕግ ድንጋጌዎች ተፈጻሚ ይሆናሉ።