ዕዳ

ሒሳቦችን በወቅቱ ያልከፈለ ሰው፣ ከባድ መዘዝ ሊያስከትልበት ይችላል።. የፋይናንስ ችግር በሚያጋጥምዎት ግዜ የዕዳ አማካሪ ማዕከላት ድጋፍ ይሰጥዎታል።

ማስጠንቀቂያ እና ዕዳ ማስፈጸሚያ

የሒሳብ ክፍያ በሰዓቱ ካልከፈሉ፣ በመደበኛነት የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ማስጠንቀቂያ (Mahnung). ይደርሰዎታል። ሆኖም አበዳሪዎች በማንኛውም ጊዜ የዕዳ ማስፈጸም (Betreibung) የማስጀመር ስልጣን አላቸው። በዚህ ግዜ ተበዳሪው ከሚመለከተው የዕዳ ማስፈጸሚያ ቢሮ (Betreibungsamt). የክፍያ ትዕዛዝ ይደርሰዋል።. ለአሰራር ሂደቱ ተጨማሪ ያስከፍላል። የዕዳ ማስፈጸሚያው ህጋዊ አይደለም ብሎ የሚያምን ማንኛውም ሰው፣ ህጋዊ ፕሮፖዛል (Rechtsvorschlag) ኃላፊነት ካለው የዕዳ ሰብሳቢ ጽሕፈት ቤት በማቅረብ መቃወም ይችላል። ማሳሰቢያ፡ ዕዳ አስፈጻሚው ደሞዝ ወይም ውድ ዕቃዎችን እንደ መያዣ አድርጎ ሊይዝ ይችላል። በተጨማሪም የዕዳ አስፈጻሚው በዕዳ ማስፈጸሚያ መዝገብ (Betreibungsregister) ውስጥ (ከፍለው እንኳን ቢሆንም) መዝግበው ይይዛሉ።. ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ አፓርታማ በሚፈልጉበት ጊዜ ችግር ሊፈጥርብዎት ይችላል።.

ዕዳ

የገንዘብ ችግር ወይም ዕዳዎች ካሉብዎት የዕዳ አማካሪ ማዕከልን (Schuldenberatungsstelle) ማነጋገር ይችላሉ። እዚያም ድጋፍ ማግኘት ይችላሉ። ባለሙያዎቹ ከምክር ፈላጊዎች ጋር አንድ ላይ በመሆን ሁኔታውን ይመለከታሉ እና መፍትሔዎችን ይፈልጋሉ። የካሪታስ ድርጅት ስም-አልባ ምክር በስልክ ይሰጣል።- “SOS ዕዳ” የምክር አገልግሎት የስልክ መስመር፣ ስልክ 0800 708 708 (ከክፍያ ነፃ) ነው። እንደስፈላጊነቱ ወደ ሌላ ቦታ ይመሩዎታል።. ከPlusminus የምክር አገልግሎት ማዕከል እርዳታ እና ጠቃሚ መረጃ ማግኘት ይችላሉ።